መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ.ም የተካሄደው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የተማሪዎች ህብረት መማክርት ምርጫ በዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የተከናወነ ሲሆን በቦታው የተገኙት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ከበደ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ ይህ ምርጫ ቀደም ሲል መካሄድ የነበረበት ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ አሁን ላይ ለመደረግ እንደበቃ ገልጸዋል።