የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው ለአፋር ወንድም ህዝብ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የዓይነት ድጋፍ አደረገ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው ለአፋር ወንድም ህዝብ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የዓይነት ድጋፍ አደረገ።

ታህሳስ 01 ቀን 2014 ዓ.ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው ለአፋር ወንድም ህዝብ በአፋር ዋና ከተማ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የአልባሳት፣ የምግብ ግብአትና ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። የአፋር ህዝብ የሀገር ሉአላዊነትን ለማስጠበቂ የከፈለው አስደናቂ መስዋዕትነትና ያደረገው ተጋድሎ እጅግ የሚመሰገን መሆኑን በማስታወስ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ይዞ ለማስቀጠል በጋራ በመደጋገፍ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበት ተገልፆአል። በተጨማሪም ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትና ማኔጅመንት ጋር በተደረገው ውይይት ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር ከወንድማማች ግንኙነት ባሻገር የስትራቴጂካዊ ግንኙነት ላይ መሰረት በማድረግ ለቀጣይ መሥራት እንደሚገባ መስማማት ላይ ተደርሷል።

ድል ለኢትዮጵያ!

ድል ለመላው ጥቁር ህዝቦች!

ውድቀት ለወራሪዎችና ፀረ-ኢትዮጵያ ሃይሎች

 

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et