ከውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰኔ 25/2016 ዓ.ም ተፈራረሟል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ ኢንስቲትዩቱ በውሃ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ባለሙያዎች ካሉት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት በመምጣቱ አመስግነው እንደሀገር እጅግ ጠቃሚ በሆኑ የውሃ ቴክኖሎጂዎች ላይ እንደ አጋር ተቋማት ተቀራርቦ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል::

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ታመነ ኃይሉ በፊርማው ወቅት እንደገለፁት ለሴክተሩ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ግብዓት እና የፖሊሲ አቅጣጫ ጠቋሚ የሆኑ የምርምርና ቴክኖሎጂ ስርፀት ስራዎችን በሰፊው አብሮ ለመስራት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሃገራችን ካሉ እምቅ አቅም ያላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ስምምነቱ ከዚህ ቀደም የነበረውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ይረዳናል ብለዋል::

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et