የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ/ም ሁለተኛ ሴሚስተር ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የትምህርት መስኮች በሁለተኛ ዲግሪ እና በሶስተኛ ዲግሪ በመደበኛው ፕሮግራም ተማሪዎች ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
College of Agriculture |
MSc in Bio-energy Science and Technology |
MSc in Agroforestry |
MSc in Gender and Family Studies |
MSc in Food Safety and Quality Management |
College of Natural and Computational Science |
MSc in Genetics |
MSc in Veterinary Parasitology |
Ph.D. in Genetics and Genomics |
Ph.D. in Applied Microbiology |
College of Medicine and Health Science |
MSc in Hospital and Health Care Administration |
MSc in Medical Biochemistry |
Institute of Technology |
MSc in Soil and Water Conservation Engineering |
MSc in Hydrology and Water Resources Engineering |
MSc in Dam Engineering |
Ph.D. in Natural Resource Engineering & Management |
College Law and Governance |
MA in Governance and Development |
MA in Public Management and Policy Development |
College of Education |
MA in Educational Research and Development |
MA in Multicultural and International Education |
Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources |
MSc in Climate Smart Agricultural Land Assessment |
MSc in Forest Resources Assessment and Monitoring |
MSc in Production Forestry |
MSc in Urban Forestry and Greening |
PhD. in Agroforestry |
Ph.D. in Forest Management |
Ph.D. in Forest Ecology and Silviculture |
Ph.D. in Wildlife Ecology (Specialization: Ornithology, Mammalogy) |
የማመልከቻ መስፈርቶች
- ለሁለተኛ ዲግሪ አመልካቾች ከታወቀ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በተመሳሳይ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ድግሪ ያለዉ/ያላት
- ለሶስተኛ ዲግሪ አመልካቾች ከታወቀ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በተመሳሳይ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክ ሁለተኛ ድግሪ ያለዉ/ያላት
- አግባብነት ካላቸዉ ተቋማት 3 የድጋፍ ደብዳቤዎች ማቅረብ የሚችል/የምትችል
- ዩኒቨርሲቲዉ የሚያወጣዉን የመግቢያ ፈተና ማለፍ የሚችል/የምትችል
- ቀደም ሲል ከተማሩበት የትምህርት ተቋም ኦፊሺያል ትራስክሪፕት ማስላክ የሚችል/የምትችል
- አግባብነት ካላቸዉ ተቋማት የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችል/የምትችል
ማሳሰቢያ፡-
- ምዝገባው የሚከናወነው በኦላይን ብቻ ሲሆን ምንም አይነት ማስረጃ በአካል ይዞ በመቅረብ ማስገባት አይቻልም፡፡
- አመልካቾች ከጥር 09-20/2014 ዓ.ም የማመልከቻ ፎርሙን በዩኒቨርስቲው ድረገጽ (https://portal.hu.edu.et) አካውንት በመፍጠር አስፈላጊዎችን መረጃዎችን መሙላት ይጠበቅባቸዋል።
- አመልካቾች የንግድ ባንክ ቁጥር 1000013481788 በመጠቀም የማመልከቻ ክፍያ 250 ብር መክፈል ይጠበቅባቸል።
- ክፍያዎትን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ማመልከቻ ፎርሙ በመመለስ ፒዲኤፍ (PDF) ፎርማት የተለወጠ የትምህርት ማስረጃዎትን፣ ባንክ የከፈሉበትን ደረሰኝ እንዲሁም የትምህርት ወጪዎን የሚሸፍንልዎት የመንግስት መስሪያ ቤት ከሆነ የተፈረመበትና ማህተም የተደረገበት የSponsorship ፎርም እና ሌሎች መረጃዎችን በማከልና በማማያዝ ምዝገባዎትን ማጠናቀቅ ይኖርብዎታል፡፡
- የመግቢያ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾ ከተማሩበት ተቋም ኦፊሺያል ትራስክሪፕታቸዉ ወደ ዩንቨርሲቲዉ ሬጅስትራርና አሉምናይ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ማስላክ የሚጠበቅባቸው ሲሆን በምዝገባ ወቅት ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ካልደረሰ መመዝገብ አይችሉም
- የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ጥር 30/ 2014 ዓ.ም በየኮሌጆቹ ይሆናል፡፡
- በመደበኛ ፕሮግራም በመንግስት ተቋማት እስፖነሰር የሚደረግ አመልካች የትምህርት ወጪው ዩኒቨርስቲው በሚጠይቀው የክፍያ መጠን መሰረት በየሴሚስተሩ በምዝገባ ወቅት ክፈያው መፈጸም ይኖርበታል።
- የተማሪዎች ቁጥር ከመቀበል አቅም በታች (ዝቅተኛ) ከሆነ የትምህርት ፕሮግራሞች የማይከፈቱ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራርና አሉሚኒ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት