የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ነው

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓም ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ነው።

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮውን ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመሰብሰብያ አዳራሽ ማካሄድ ጀምሯል::

እስከ ነገ የሚቀጥለውን የውይይት መድረክ የከፈቱት የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር አያኖ በራሶ ሲናገሩ በተለይ መሻሻል ያለባቸው ነጥቦች ላይ የበለጠ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አመላክተዋል:: ፕሬዚደንቱ እንዳሉት ከተለመዱ የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማዎች ወጣ ብለን በተለይ የመውጫ ፈተናን እንዲሁም ውጤትን ማዕከል ያደረገ የዕቅድ አፈፃፀም እና የተሻለ የሪፖርት ዝግጅትና አቀራረብ ላይ እናተኩራለን ብለዋል::

 

በማስከተልም እስካሁን ድረስ በዩኒቨርሲቲያችን የሚያጋጥሙንን የተለያዩ ተግዳሮቶች በጋራ በመስራት በጥንካሬ የመወጣት ልምዱ እንዳለን አይተናል እና አሁን ደግሞ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በሚያስችለን ሽግግር ወቅት ላይ እንደመሆናችን በጣም ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል:: "ዘንድሮ ባለው የወቅታዊ ጉዳዮች መደራረብ የተነሳ ይሄንን መድረክ ለማዘጋጀት ራሱ ካለፈው ሳምንት ወደዚህኛው ለማምጣት ተገደናል:: ሆኖም ግን አሁን የፈተና ወቅት ስለሆነ በፈተና አሰጣጥ ላይ ምንም አይነት ክፍተት እንዳይፈጠር ትምህርት ክፍሎች ላይ የማስተባበር ስራው በተሳካ ሁኔታ እንዲሰራበት ይጠበቃል" በማለት አቅጣጫ ሰጥተዋል::

 

በመድረኩ የየኮሌጆቹ ዲኖች: የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር: የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር እንዲሁም የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር የግማሽ አመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ተሳታፊዎች በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ጥያቄያቸውን እያነሱ ነው:: የአስተያየትና ጥያቄውን የውይይት መርሃግብር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንትና የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት የሚመሩት ሲሆን መድረኩ እስከ ነገ ግማሽ ቀን ድረስ እንደሚቀጥል ታውቋል::

Contact Us

Office of External Relations & Communications 
Phone:  +251 46 220 5168
International Relations
Public Relations 

Touch Us

Registrar Contact 

Registrar Directorate 
Phone: 0462200229
Email: registrar@hu.edu.et